Official Announcements From Badr
በአንበጣ መንጋ ለተጎዱ አካባቢዎች ድጋፍን ስለመጠየቅ
Posted by Badr Ethiopia on

በአንበጣ መንጋ ለተጎዱ አካባቢዎች ድጋፍን ስለመጠየቅ በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለዉ የአንበጣ መንጋ ምክንያት በተለያዩ አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ሰምተናል አይተናልም። በተለይ በአማራ ክልል ወሎ አካባቢ የሚገኙ ቁጥራቸው በዛ ባሉ ቀበሌዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች እንዲሁም የትግራይ ክልልን ጨምሮ በአንበጣው መንጋ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸዉ አካባቢዎች ላይ ሰብላቸው ከጥቅም ውጭ ሆኗል። የገበሬው ሁኔታ እንደምናዉቀው አመት ለፍቶ ጠብቆ የሚሰበስበው ሰብሉን አጥቶ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ በችግር ላይ ይገኛል። ምንም እንኳን ጥፋቱን ለመታደግ በቀላል የሚታሰብ እንኳ ባይሆንም መንግስት በደረጃዉ ይህን መሰል የሰብል ዉድመት ዳግም በሀገሪቱ እንዳይከሰት በቋሚነት ጥናት አድርጎ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መቅረፍ እንደሚገባዉ ...
ታዋቂዉ ዓሊም ሸይኽ መሐመድ ዓሊ አደም ወደ አኼራ ሄዱ
Posted by Badr Ethiopia on

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን ኢትዮጵያ ታዋቂዉን ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዓሊ አደምን አጣች ኢትዮጵያዊዉ ታላቅ ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዓሊ አደም ወደ አኼራ መሄዳቸዉን የሰማነዉ በታላቅ ሀዘን ነዉ። ኑሮአቸዉን በሳዑዲ ያደረጉ እዉቁ ሸይኽ ሙሐመድ ዓሊ ለብቃታቸዉ በዓለም ደረጃ እዉቅናን ያገኙ ታላቅ ስመ ጥር ዓሊም ነበሩ። በርካታ የጻፉዋቸዉ ኪታቦች እንዳላቸዉም ይታወቃል ። ሀገራችን ኢትዮጵያ ብርቅዬ ዓሊሞች ያሏት ቢሆንም በወጉ ሳንጠቀምባቸዉ በሀገር ዉስጥ በሚደርስባቸዉ አሉታዊ ተጽእኖ ሳቢያ እምነታቸዉን በአግባቡ ለመተግበር ሲሉ በየሀገራቱ በስደት ለመኖር እየተገደዱ ናቸዉ። ዓሊሞቻችንን መጠበቅ የሁላችን ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ እያሳሰብን በተለይ የሚመለከታቸዉ ክፍሎች በሁለንተናዊ መልኩ ተጠናክረዉ ለዉጥ ሊያመጣ በሚችል ሁናቴ ለዓሊሞቻችን ልዩ...
የአረብኛ ቋንቋም ይታሰብበት እንላለን
Posted by Badr Ethiopia on

የአረብኛ ቋንቋም ይታሰብበት እንላለን በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ ለዉጦች አበረታች ከመሆናቸዉ አልፎ እየታዩ ያሉ ተግባራትም ሊመሰገኑ ይገባል የሚል እምነት አለን ። በቅርቡ በተለያዩ ክልሎች በትምህርት ቤቶች ደረጃ ሊሰጡ ይገባሉ በሚል የተለያዩ የሀገር ዉስጥ እና የዉጭ ቋንቋዎችን በትምህርት ቤቶች ደረጃ ለመስጠት ቅድመ ሁኔታዎችን እያመቻቹ እንደሆነ መገለጻቸዉ ይታወቃል። ይህም ሂደት እጅግ በጣም አበረታች መሆኑን በመግለጽ ለአፈጻጸሙ ስኬታማነት ትኩረት ይሰጠዉ እንላለን ። በተጨማሪነት ይሰጣሉ ተብለዉ ከተጠቀሱ ቋንቋዎች በተጓዳኝ ትኩረት ሊሰጠዉ ይገባል የምንለዉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ደረጃ የተናጋሪ ቁጥር ካላቸዉ ቋንቋዎች አንዱ የሆነዉ የአረብኛ ቋንቋ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን በተጨማሪነት ይሰጣሉ ተብለዉ ከተጠቀሱ ቋንቋዎች ዉስጥ አለመካተቱ እጅጉን አሳስቦናል። በተለይ በሀገራችን...
ሱልጣን ሀንፈሬ ዓሊሚራህ ወደ አኼራ ሄዱ
Posted by Badr Ethiopia on

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን ሱልጣን ሀንፈሬ በአሳይታ ከተማ ተወልደዉ በአዲስ አበባና በአሜሪካ ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ ቆይተዉ በኋላም ወደ ሀገራቸዉ በመመለስ ከአባታቸዉ ጎን በመሆን አገራቸዉንና ወገናቸዉን ሲያገለግሉ ቆይተዋል። አባታቸዉም “ እንኳን እኛ ግመሎቻችንም የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ያዉቃሉ’’ በማለት ሀገር ወዳድነታቸውን በዚህ መልኩ ገልጸዉታል። ወላጅ አባታቸዉ ሱልጣን አሊሚራህ ሲሞቱም ሱልጣኔነቱን ተረክበዉ ቆይተዋል። የ1966 ቱ ወታደራዊዉ መንግስትም ስልጣኑን ተረክቦ ሶሻሊዝምን ማራመድ በጀመረበት ወቅት ተቃዉሞአቸዉን ቀጥለዉ የአፋር ነጻ አዉጪ ግንባርን በማቋቋም እስከ 1983 ድረስ የትጥቅ ትግል ሲያካሄዱም ቆይተዋል። በወቅቱም የተደረገዉን የመንግስት ለዉጥ ተከትሎ ወደ አገራቸዉ ለመመለስ በቅተዋል። ከ2001 እስከ 2006 በኩዌት የኢትዮጵያ መንግስት ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር በመሆን እያገለገሉ...
በስልጢ ዞን የጎርፍ አደጋ ተከሰተ
Posted by Badr Ethiopia on

በስልጢ ዞን የጎርፍ አደጋ ተከሰተ በዘንድሮ ዓመት በሀገራችን በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ በተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ መከሰቱን ተከትሎ ከሚወድመዉ ንብረት ባሻገር በርካታ ዜጎች ከቀዬአቸዉ መፈናቀላቸዉ ሲሆን በተለይ በአፋር ክልል ለተፈጠረዉ ዉድመት እኔም አፋር ነኝ በሚል መርሀ ማህበረሰቡ እያደረገ ያለዉ ድጋፍ እጅግ በጣም አበረታች ነዉ። ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባልም እያልን ችግሩ በተጨማሪነት በደቡብ ክልል ዉስጥ በሚገኘዉ የስልጢ ዞንም ባለፉት ዓመታትም በተመሳሳይ ወቅት ጎርፍ ከሚያጠቃቸዉ አካባቢዎች አንዱ እንደሆን የሚታወቅ ሲሆን በዘንድሮዉም ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋርጦበታል። በቅርብ ጊዜያት ከኮቪድ 19 ጀምሮ ማህበረሰቡን ለተለያዩ ድጋፎች ማስቸገራችን የሚታወቅ ነዉ። አንዱ ችግራችን ሳይቀረፍ ሌላዉ እየተተካብን ይገኛል። ይህም የሚያሳየዉ ብዙ ያልተሰሩ ነገሮች እንዳሉ እና በተለይ...