News feed From Diaspora
ዶክተር አብይ አህመድ አሊ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚ በመሆናቸው ከበድር ኢትዮጵያ የተሰጠ የደስታ መግለጫ!
Posted by Badr Ethiopia on
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነዉ ዶክተር አብይ አህመድ አሊ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚ በመሆናቸው ከበድር ኢትዮጵያ የተሰጠ የደስታ መግለጫ! ዶክተር አብይ አህመድ አሊ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚ በመሆናቸው በድር ኢ ትዮጵያ የተሰማውን ደስታ በድርጅቱ መሪወችና በአባላቱ ስም የተሰማውን ደስታ ለኢትዮጵያ መንግስና ሕዝብ በኩራትና በተስፋ ይገልጻል። ይህ ዓለም ዓቀፍ የበጎ እይታ ግንዛቤ ለአገራችን ሕዝቦችና ፖሊቲከኞች የመልካም መንፈስ መፍለቂያና ማጠናከሪያ እንዲሆንም በጽኑ እንመኛለን። የዶክተር አብይ አህመድ ለዚህ እድል ተመራጭ መሆን ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም ኩራት ነው። ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ ወደ ስልጣን ከመጡበት እለት ጀምሮ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ቀንድ የነበረውን ሽኩቻና አለመረጋጋት ለማርገብና ሰላምን ለማስፈን ብዙ ደፋ ቀና ያሉና የጣሩ ብሎም...
የበድር ኢትዮጵያ የጉባኤ የአቋም መግለጫ
Posted by keder nuru on

በድር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሙስሊሞች ድርጅት በ2018 በሰላም ፋዉንዴሽን ኮምዩኒቲ አዘጋጅነት ከጁላይ 26 እስከ 29 በተካሄደዉ 18 ኛዉ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ዶክተር አቢይ አህመድ ፤ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር የክቡር ዶክትሬት አቶ ለማ መገርሳ እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና ኢንጂነር በድሩ ሁሴን ሌሎችም ዉድና የተከበሩ ኡስታዞቻችን በተሳተፉበት በዚሁ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ የተሰጡ ትምህርቶች እና የተላለፉ የመፍትሄ ሀሳቦችን ግምት ዉስጥ በማስገባት በጉባኤዉ ማጠቃለያ የሚከተለዉን ባለ ዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ በጋራ አዉጥተናል። 1. ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር አቢይ አህመድ አሊ እና አመራራቸዉ በሚተገብሩት ፈጣን የለዉጥ ሂደት ሀገራችን ወደ ተሻለ...
የጋራ አቋም መግለጫ
Posted by keder nuru on

የጋራ አቋም መግለጫ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነዉእንደሚታወቀው በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ዘርፈ ብዙ የሆነውን የማህበረሰባችንን ሃይማኖታዊ እና ማህበራዊ ፍላጎቶች ለማሟላት ተደራጅተን ስንንቀሳቀስ ቆይተናል፡፡ በመካከላችን ማጎልበት የምንፈልገውን መንፈሳዊ ትስስር በሚያሳድጉ ስራዎች ላይ ከማተኮራችን በተጨማሪ በሀገርቤት ሙስሊሙን ማህበረሰብ በሚመለከቱ እና አጠቃላይ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የድርሻችንን ለመወጣት ስንጥር ቆይተናል፡፡ እነዚህን የመሰሉ ክንዋኔዎችን በተደራጀ መልኩ ለመስራት በምናደርገው ጥረት በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደቻልነው ሁሉ በረጅም ዓመታት ጉዟችን ውስጥ የአካሄድ ልዩነቶች እየተፈጠሩ ሂደታችን ሲገታ እና በመካከላችን ቅራኔዎች ሲፈጠሩ መቆየታቸውም አልቀረም፡፡ እነዚህን ክፍተቶች በግዜ ለማጥበብ የተደረጉ የውስጥ ጥረቶች ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ባለመቻላቸው በማህበረሰባችን ጉዳይ ላይ ልናበረክት የምንችለውን አስተዋፅኦ ከማስተጓጎሉ...
“ትውልድን በጋራ እንታደግ”
Posted by keder nuru on